ወደ ይዘቱ ዝለል
ቀጥታ ዝማኔ
ሀሁኒውስ

ግልጽና የታመነ ዜና

" ልዩ ድል ነው ፤ በቡድኔ ኮርቻለሁ " ፋብያን ሁርዜለር

ምንጭ፦ TIKVAH | Ethiopia Sport

·

አጋራXFacebookTelegramLinkedIn
" ልዩ ድል ነው ፤ በቡድኔ ኮርቻለሁ " ፋብያን ሁርዜለር
" ልዩ ድል ነው ፤ በቡድኔ ኮርቻለሁ " ፋብያን ሁርዜለር

የብራይተኑ አሰልጣኝ ፋብያን ሁርዜለር አርሰናል ላይ ከተቀዳጁት ድል በኋላ “ በቡድኔ ኮርቻለሁ ” ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

“ ልዩ ድል ነው “ ሲሉ የገለፁት ፋብያን ሁርዜለር “ ያሸነፍነው የእንግሊዙን ምርጥ ቡድን ስለሆነ ብቻ ሳይሆን ያሳየነው አቋም ልዩ ያደርገዋል ” ብለዋል።

አክለውም “ በቡድኔ በጣም ኮርቻለሁ ፤ ለተጋጣሚያችን በጣም አስፈሪ ነበርን " በማለት ተናግረዋል።

ስለ ቡድናቸው አምበል ፓስካል ግሮስ ያነሱት አሰልጣኙ “ ግቦችን በማስቆጠር የሚደሰት ” ሲሉ ገልፀውታል።

“ ሙሉ በሙሉ ልታምነው የምትችለው እና በዙሪያው ያሉትን የቡድን አጋሮቹን በእጅጉ የተሻሉ የሚያደርግ ተጫዋች ነው “ ሲሉ አወድሰውታል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe

ተዛማጅ ታሪኮች