ወደ ይዘቱ ዝለል
ቀጥታ ዝማኔ
ሀሁኒውስ

ግልጽና የታመነ ዜና

አርጀንቲና ግማሽ ፍፃሜውን ተቀላቀለች !

ምንጭ፦ TIKVAH | Ethiopia Sport

·

አጋራXFacebookTelegramLinkedIn
አርጀንቲና ግማሽ ፍፃሜውን ተቀላቀለች !
አርጀንቲና ግማሽ ፍፃሜውን ተቀላቀለች !

የአለም ሻምፒዮናዋ አርጀንቲና በጭማሪ ሰላሳ ደቂቃ ባስቆጠሩት ግብ ስዊዘርላንድ 3ለ1 አሸንፈዋል።

ማክ አሊስተር ፣ ጁሊያን አልቫሬዝ እና ላውታሮ ማርቲኔዝ የአርጀንቲናን የማሸነፊያ ጎሎች ሲያስቆጥሩ ንዶዬ ስዊዘርላንድ አቻ ማድረግ ችሎ ነበር።

ስዊዘርላንድ በጨዋታው ኢምቦሎ በሁለት ቢጫ ካርድ ከሜዳ መውጣቱን ተከትሎ ከ 7️⃣2️⃣ኛ ደቂቃ በኃላ በአስር ልጅ ጨዋታውን ጨርሰዋል።

አርጀንቲና በዘንድሮው የአለም ዋንጫ አስራ ሰባት ጎሎችን በማስቆጠር ቀዳሚዋ ሀገር ሆናለች።

የአለም ሻምፒዮናዋ አርጀንቲና በቀጣይ እሮብ የግማሽ ፍፃሜ መርሐ ግብሯን ከ እንግሊዝ ጋር ታደርጋለች።

ሊዮኔል ሜሲ ምን አስመዘገበ ?

- ሊዮኔል ሜሲ ማክ አሊስተር ላስቆጠረው ጎል አመቻችቶ ኳስ አቀብሏል።

- ሜሲ በአለም ዋንጫው 1️⃣0️⃣ኛው ለጎል የሚሆን ኳስ አመቻችቶ ያቀበለ ሲሆን በታሪክ ቀዳሚው ተጫዋች ያደርገዋል።

- ሊዮኔል ሜሲ በዘንድሮው የአለም ዋንጫ በ 1️⃣0️⃣ ጎሎች ላይ ቀጥተኛ ተሳትፎ ማድረግ ችሏል።

- ሊዮኔል ሜሲ በአለም ዋንጫው የምንጊዜውም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ እንደሆነ ይታወቃል።

@tikvahethsport @kidusyoftahe

ተዛማጅ ታሪኮች