“ አጃኢባ የቀረችው የአለም አትሌቲክስ መልዕክት ልኮልን ነው ” ኮማንደር ስለሺ ስህን

“ አጃኢባ የቀረችው የአለም አትሌቲክስ መልዕክት ልኮልን ነው ” ኮማንደር ስለሺ ስህን
በአሜሪካ በሚካሄደው የወጣቶች የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ለመሳተፍ ዝግጅት ላይ የነበረችው አትሌት አጃኢባ አሊዬ ወደ ስፍራው አላቀናችም።
በ 400ሜ ጥሩ ውጤት ያላት አትሌት አጃይባ አሊዬ በውድድሩ ለሜዳልያ ተጠብቃ ነበር።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ኮማንደር ስለሺ ስህን አትሌቷ በምን ምክንያት እንደቀረች ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ኮማንደር ስለሺ ስህን በሰጡት አስተያየት “ አጃኢባ የአጭር ርቀት ሯጭ እንደመሆኗ በልዩነት ነገሮችን አመቻችተን ስናዘጋጃት ነበር ” ብለዋል።
“ ነገርግን የአለም አትሌቲክስ ህክምና ቡድን አትሌቷ እንዳትመጣ የሚል መልዕክት ስለላከ ልትቀር ችላለች “ ሲሉ ኮማንደር ስለሺ ስህን ተናግረዋል።
ሁሉም አትሌቶች የዶፒንግ እና የሆርሞን ምርመራ ማድረጋቸውን ያነሱት ስለሺ ስህን “ የህክምና መረጃው የተላከው በአትሌቶቹ ኢሜል ነው “ ብለዋል።
አትሌት አጃኢባ አሊዬ ተጨማሪ መረጃዎች እንደተላከላት እና በፌዴሬሽኑ ቢሮ ተገኝታ በዚህ ምክንያት እንደቀረች ከህክምና ቡድኑ ጋር መነጋገሯን ጨምረው ተናግረዋል።
የመረጃው ባለቤት ፋና ቴሌቪዥን ነው።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
በአሜሪካ በሚካሄደው የወጣቶች የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ለመሳተፍ ዝግጅት ላይ የነበረችው አትሌት አጃኢባ አሊዬ ወደ ስፍራው አላቀናችም።
በ 400ሜ ጥሩ ውጤት ያላት አትሌት አጃይባ አሊዬ በውድድሩ ለሜዳልያ ተጠብቃ ነበር።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ኮማንደር ስለሺ ስህን አትሌቷ በምን ምክንያት እንደቀረች ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ኮማንደር ስለሺ ስህን በሰጡት አስተያየት “ አጃኢባ የአጭር ርቀት ሯጭ እንደመሆኗ በልዩነት ነገሮችን አመቻችተን ስናዘጋጃት ነበር ” ብለዋል።
“ ነገርግን የአለም አትሌቲክስ ህክምና ቡድን አትሌቷ እንዳትመጣ የሚል መልዕክት ስለላከ ልትቀር ችላለች “ ሲሉ ኮማንደር ስለሺ ስህን ተናግረዋል።
ሁሉም አትሌቶች የዶፒንግ እና የሆርሞን ምርመራ ማድረጋቸውን ያነሱት ስለሺ ስህን “ የህክምና መረጃው የተላከው በአትሌቶቹ ኢሜል ነው “ ብለዋል።
አትሌት አጃኢባ አሊዬ ተጨማሪ መረጃዎች እንደተላከላት እና በፌዴሬሽኑ ቢሮ ተገኝታ በዚህ ምክንያት እንደቀረች ከህክምና ቡድኑ ጋር መነጋገሯን ጨምረው ተናግረዋል።
የመረጃው ባለቤት ፋና ቴሌቪዥን ነው።
@tikvahethsport @kidusyoftahe


