ወደ ይዘቱ ዝለል
ቀጥታ ዝማኔ
ሀሁኒውስ

ግልጽና የታመነ ዜና

“ እኛ ቀይ ካርድ ነው ያሰረዝነው እንግሊዝ ግን ከዚህ የከፋ አድርጋለች ”

ምንጭ፦ TIKVAH | Ethiopia Sport

·

አጋራXFacebookTelegramLinkedIn
“ እኛ ቀይ ካርድ ነው ያሰረዝነው እንግሊዝ ግን ከዚህ የከፋ አድርጋለች ”
እኛ ቀይ ካርድ ነው ያሰረዝነው እንግሊዝ ግን ከዚህ የከፋ አድርጋለች ”

የአሜሪካ አለም ዋንጫ አዘጋጅ ግብረ ኃይል ሀላፊ አንድሬው ጁላኒ ዶናልድ ትራምፕ ቀይ ካርድ ማሰረዛቸውን “ ስህተትን ማረም ” ሲሉ ገልፀውታል።

ሀላፊው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ስልክ መደወላቸውን “ ትክክል ” ሲሉ የደገፉ ሲሆን “ እንግሊዝ ግን የከፋ አድርጋለች “ ሲሉ ወቅሰዋል።

የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ኬር ስታርመር የጨዋታ ሰዓት ማስቀየራቸውን የገለፁት ሀላፊው ይሄ ከእኛ የከፋ ነው ሲሉ ተደምጠዋል።

እንዴት የከፋ እንዳሉ ያስረዱት ሀላፊው “ በሜክሲኮ ደጋፊዎች ስለሞቱ ተመሳሳይ አደጋ እንዳይከሰት የጨዋታ ሰዓት ሊቀየር ነበር እንግሊዝ አሻፈረኝ ብላለች ” ብለዋል።

" ይሄ ነው አሳዛኝ ድርጊት " የሚሉት ሀላፊው “ የሰዎችን ህይወት አደጋ ላይ ጥለዋል ይሄ ከሜዳ ላይ ድርጊት የበለጠ አሳሳቢ ነው “ ሲሉ ተደምጠዋል።

ይሁን እንጂ የእንግሊዝ እና ሜክሲኮ ጨዋታ ሰዓት ሊቀየር የነበረው በአየር ሁኔታ ምክንያት መሆኑ ሲዘገብ ነበር።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe

ተዛማጅ ታሪኮች