ወደ ይዘቱ ዝለል
ቀጥታ ዝማኔ
ሀሁኒውስ

ግልጽና የታመነ ዜና

የአርጀንቲና ፕሬዝዳንት ተጨዋቾቹን ተቹ !

ምንጭ፦ TIKVAH | Ethiopia Sport

·

አጋራXFacebookTelegramLinkedIn
የአርጀንቲና ፕሬዝዳንት ተጨዋቾቹን ተቹ !
የአርጀንቲና ፕሬዝዳንት ተጨዋቾቹን ተቹ !

የአርጀንቲናው ፕሬዝዳንት ዣቪየር ሚሌ የሀገሪቱን ብሔራዊ ቡድን ተጨዋቾች ድርጊት ተችተዋል።

የአርጀንቲና ተጨዋቾች ትላንት እንግሊዝን ካሸነፉ በኋላ ፖለቲካዊ ይዘት ያለው አርማ አስመልክተው ነበር።

ተጨዋቾቹ ያነሱት የፖለቲካ ጉዳይ “ በዲፕሎማሲ ጥበብ እንጂ በተራ ፅሁፍ የሚመለስ አይደለም "ሲሉ ተችተዋል።

“ ይሄ እግርኳስ ብቻ ነው “ ያሉት ፕሬዝዳንቱ ጉዳዩን አታወሳስቡ ተጨዋቾቹ የዲፕሎማሲ አካል አይደሉም ብለዋል።

ድርጊቱን " ኃላፊነት የጎደለው “ ሲሉ ፕሬዝዳንት ዣቪየር ሚሌ ገልጸዋል።

የእንግሊዝ ፖለቲከኞች በድርጊቱ የተሳተፉ የአርጀንቲና ተጨዋቾች እንዲቀጡ ለፊፋ ደብዳቤ መፃፋቸውን ገልፀዋል።

ተጨዋቾቹ ያስመለከቱት ፅሁፍ እንግሊዝ እና አርጀንቲና ከዚህ በፊት በይገባኛል ጥያቄ የተዋጉበትን ደሴት ይመለከታል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe

ተዛማጅ ታሪኮች