ወደ ይዘቱ ዝለል
ቀጥታ ዝማኔ
ሀሁኒውስ

ግልጽና የታመነ ዜና

የደቡብ ኮርያ ፕሬዝዳንት ትዕዛዝ ሰጡ !

ምንጭ፦ TIKVAH | Ethiopia Sport

·

አጋራXFacebookTelegramLinkedIn
የደቡብ ኮርያ ፕሬዝዳንት ትዕዛዝ ሰጡ !
የደቡብ ኮርያ ፕሬዝዳንት ትዕዛዝ ሰጡ !

የደቡብ ኮርያ ፕሬዝዳንት ሊ ጄ ሚዩንግ የሀገሪቱ ስፖርት ሚንስቴር ብሔራዊ ቡድኑ ያሳየውን ደካማ እንቅስቃሴ መርምሮ ሪፖርት እንዲያቀርብ ትዕዛዝ ሰጥተዋል።

የብሔራዊ ቡድኑ ዋና አሰልጣኝ ሆንግ ሚዩንግ በገዛ ፍቃዳቸው ከሀላፊነት መልቀቃቸው ተገልጿል።

ፕሬዝዳንት ሊ በተመዘገበው ውጤት "ግራ እንደተጋቡ" በመግለፅ
ፌዴሬሽኑ ዋና አሰልጣኝ ሆንግን መሾማቸውን ተችተዋል።

ፕሬዝዳንቱ አሰልጣኝ ቅጥር ሲፈፀም "ብቃት" ቅድሚያ እንዳልተሰጠው ገልፀዋል።

አሰልጣኙ ከሀፊነት በገዛ ፈቃዳቸው ከለቀቁ በኃላ “ በአለም ዋንጫው ለተመዘገበው ደካማ ውጤት ሙሉ ሀላፊነቱን እኔ እወስዳለሁ “ ብለዋል።

ፕሬዝዳንቱ በሰጡት መመሪያም “ ከግብር ከፋዩ ህዝብ ላይ በጀት ተፈቅዶላቸው ለተመዘገበው ውጤት ስፖርት ሚንስትሩ መርምሮ ያሳውቀኝ “ ሲል ጠይቀዋል።

@tikvahethsport @kidusyoftahe

ተዛማጅ ታሪኮች