ወደ ይዘቱ ዝለል
ቀጥታ ዝማኔ
ሀሁኒውስ

ግልጽና የታመነ ዜና

“ ዳኛው ማንም ሰው ህግ እንዲጥስ መፍቀድ የለበትም ” ሉዊስ ዴ ላ ፉንቴ

ምንጭ፦ TIKVAH | Ethiopia Sport

·

አጋራXFacebookTelegramLinkedIn
“ ዳኛው ማንም ሰው ህግ እንዲጥስ መፍቀድ የለበትም ” ሉዊስ ዴ ላ ፉንቴ
“ ዳኛው ማንም ሰው ህግ እንዲጥስ መፍቀድ የለበትም ” ሉዊስ ዴ ላ ፉንቴ

የስፔን ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሉዊስ ዴ ላ ፉንቴ የአርጀንቲና የሀይል አጨዋወት አሳስቧቸው እንደሆነ ተጠይቀው ነበር።

አሰልጣኙ በምላሻቸው በዚህ ጉዳይ “ የዳኛው የጨዋታ አመራር አቅም “ የራሱን አይነተኛ ሚና ይጫወታል ሲሉ ተደምጠዋል።

“ ዳኛው ቸልተኛ እንዳይሆን " ሲሉ ያሳሰቡት አሰልጣኙ “ ማንም ሰው ህጉን እንዲያልፍ እና የጨዋታ ደንብ እንዲጣስ መፍቀድ የለበትም " ብለዋል።

አክለውም “ በዳኞቹ ሙሉ እምነት አለኝ ” ያሉ ሲሆን “ ምን አይነት ጨዋታ መጫወት እንዳለብንም በደንብ እናውቃለን " ሲሉ ገልጸዋል።

ፔድሪን ዳግም ተጠባባቂ ያደርጉ እንደሆነ የተጠየቁት አሰልጣኙ “ ከዚህ የበለጠ ውሳኔም አሳልፌያለሁ “ ብለዋል።

“ እኛ ቡድን ነን ቡድን ማለት ደግሞ ሁሉንም ተጨዋቾች መጠቀም ማለት ነው ሁሉም ተጨዋቾች አስፈላጊ ናቸው ” ሲሉ ጨምረው ተናግረዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe

ተዛማጅ ታሪኮች