“ ፈረንሳይ አንድም ፈረንሳዊ ባይኖርም ጥሩ ስብስብ አላት ”

“ ፈረንሳይ አንድም ፈረንሳዊ ባይኖርም ጥሩ ስብስብ አላት ”
የቀድሞ የስፔን ጠቅላይ ሚኒስቴር ማሪያኖ ራጆይ በሰጡት አስተያየት ምክንያት ከፍተኛ ትችት ቀርቦባቸዋል።
የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የስፔን የግማሽ ፍፃሜ ተፋላሚ ፈረንሳይ ላይ የዘረኝነት ጥቃት አድርሰዋል በሚል ተተችተዋል።
የሀገሪቱ የቀድሞ መሪ ማሪያኖ ራጆይ “ ፈረንሳይ አንድም ፈረንሳዊ የሌለበት ትልቅ ስብስብ ይዛለች “ ብለው ነበር።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የቀድሞ መሪው ስፔን ቤልጂየምን ስታሸንፍ " ሁለት " ደስታ ተሰምቶኛል ብለዋል።
“ አንዱ ደስታ ስፔናዊ ስለሆንኩ ያገኘሁት ነው ሁለተኛው ግን የቤልጅየም ተጨዋቾች “ ቀይ ሰይጣኖች " ስለሚባሉ ሰይጣን ስለማልወድ ስለተሸነፉ ተደስቻለሁ “ ሲሉ ተደምጠዋል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
የቀድሞ የስፔን ጠቅላይ ሚኒስቴር ማሪያኖ ራጆይ በሰጡት አስተያየት ምክንያት ከፍተኛ ትችት ቀርቦባቸዋል።
የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የስፔን የግማሽ ፍፃሜ ተፋላሚ ፈረንሳይ ላይ የዘረኝነት ጥቃት አድርሰዋል በሚል ተተችተዋል።
የሀገሪቱ የቀድሞ መሪ ማሪያኖ ራጆይ “ ፈረንሳይ አንድም ፈረንሳዊ የሌለበት ትልቅ ስብስብ ይዛለች “ ብለው ነበር።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የቀድሞ መሪው ስፔን ቤልጂየምን ስታሸንፍ " ሁለት " ደስታ ተሰምቶኛል ብለዋል።
“ አንዱ ደስታ ስፔናዊ ስለሆንኩ ያገኘሁት ነው ሁለተኛው ግን የቤልጅየም ተጨዋቾች “ ቀይ ሰይጣኖች " ስለሚባሉ ሰይጣን ስለማልወድ ስለተሸነፉ ተደስቻለሁ “ ሲሉ ተደምጠዋል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe


