በኢትዮጵያ የወንጀል ፍትህ ሥርዓት ውስጥ ወንጀል ፈጽመው የታረሙ ግለሰቦች በድጋሚ ወደ ወንጀል ድርጊት የመመለሳቸው ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ጥናት አመልክቷል።
ምንጭ፦ TIKVAH Ethiopia
·

በኢትዮጵያ የወንጀል ፍትህ ሥርዓት ውስጥ ወንጀል ፈጽመው የታረሙ ግለሰቦች በድጋሚ ወደ ወንጀል ድርጊት የመመለሳቸው ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ጥናት አመልክቷል።
👉 በጥናቱ ከተካተቱና ወንጀል ፈጽመው ታርመው ከወጡት ታራሚዎች ውስጥ 94 በመቶዎቹ ከ5 አመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ በሌላ ወንጀል በድጋሚ ወደማረሚያ ቤት የተመለሱ ናቸው።
በኢትዮጵያ የወንጀል ፍትህ ሥርዓት ውስጥ ወንጀል ፈጽመው የታረሙ ግለሰቦች በድጋሚ ወደ ወንጀል ድርጊት የመመለሳቸው ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ እንደሚገኝና ይህንን ለመግታት የተቀናጀ የመረጃ አያያዝና የህግ ማዕቀፍ እንደሚያስፈልግ የኢትዮጵያ የህግ እና ፍትህ ኢንስቲትዩት ያከናወነው ጥናት አመልክቷል።
ኢንስቲትዩቱ አመታዊ የጥናትና ምርምር ማጽደቂያ መርሃ ግብሩን ያከናወነ ሲሆን በመድረኩ "የወንጀል ደጋጋሚነት እና የማረሚያ ቤት ሚና በኢትዮጵያ፣ የሕግ ማዕቀፍ እና አተገባበር ስርዓት" የተሰኘ ጥናቱን ይፋ አድርጓል።
በፌደራል ማረሚያ ቤቶች ላይ ትኩረቱን አድርጎ የቀረበው ይህ ጥናት፣ ወንጀለኞች ታርመውና ታንጸው ሰላማዊ ዜጋ እንዲሆኑ ከማድረግ አንጻር አሁንም ሰፊ ክፍተቶች መኖራቸውን አመልክቷል።
ቀደም ሲል በተፈጸመ ወንጀል፣ ቅጣት በተሰጠ ወይም በይቅርታ ቀሪ እንዲሆን በተደረገ በአምስት አመት ጊዜ ውስጥ ስድስት ወር የሚያስቀጣ አዲስ ወንጀል ሰርቶ መገኘት የወንጀል ደጋጋሚነት የሚባል ሲሆን በወንጀል ፍትህ ስርዓት ውስጥ ማረሚያ ቤቶች ታራሚዎችን እያረሙ ስለመሆን ወይም አለመሆናቸው የሚለይበት ዋናኛ መለኪያ ነው።
ይሁን እንጂ በጥናቱ ከተካተቱት 127 የወንጀል ድጋሚ ፈጻሚዎች መካከል ከአምስት ዓመት ቆይታ በኋላ በወንጀል ድርጊት የተገኙት 5.6 በመቶዎቹ ብቻ ሲሆኑ ቀሪዎቹ ማለትም 94.4 በመቶ የሚሆኑት ከአምስት ዓመት በታች በሆነ ጊዜ ወደ ማረሚያ ቤት ተመልሰዋል ይህም የፌደራል ማረሚያ ቤቶች ታራሚዎችን የማረም ሂደት ላይ ውጤታማነት እንደማይታይበት አመላካች ሆኗል።
የጥናቱ ውጤት በዝርዝር ሲታይ 57.9 በመቶ የሚሆኑት ለሁለተኛ ጊዜ ወደ ማረሚያ ቤት የተመለሱ ሲሆኑ፣ 31 በመቶዎቹ ደግሞ ለሦስተኛ ጊዜ የተፈረደባቸው ናቸው።
ከእስር ከተፈቱ በኋላ ወደ ወንጀል ለመመለስ የሚወስድባቸውን ጊዜ በተመለከተ፣ 36.5 በመቶ የሚሆኑት ከ2 እስከ 5 ዓመት ባለው ጊዜ ውስጥ ሲመለሱ፣ 23 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ ከ6 ወር እስከ 1 ዓመት ባለው አጭር ጊዜ ውስጥ በድጋሚ ወንጀል ፈጽመው ይገኛሉ።
17.5 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ ከ6 ወር በታች በሆነ ጊዜ ወደ ወንጀል መመለሳቸውን ውጤቱ ያሳያል።
በተጨማሪም፣ ታራሚዎቹ ቀደም ሲል ተከሰው ከተቀጡበት ወንጀል (52 በመቶ ዝርፊያ/ስርቆት) ጀምሮ፣ በአሁኑ ጊዜ ተይዘው ወደ ማረሚያ ቤት እንዲገቡ ካደረጋቸው አዲስ ወንጀል (53.6 በመቶ ዝርፊያ/ስርቆት) ድረስ ተመሳሳይ የወንጀል ዓይነት ደጋግመው መፈጸማቸው በጥናቱ ተመዝግቧል።
የተቀሩት አደንዛዥ ዕፅ መጠቀም እና ማዘዋወር ፣ውንብድና ፣ የግብር ስወራና ማጭበርበር ፣ ህገወጥ የሰዎች ዝውውር ፣የሙስና ወንጀሎች እና ሌሌችም ወንጀሎች ይገኙበታል።
በጥናቱ በድጋሚ ወንጀል እንዲፈጽሙ ካደረጓቸው ምክንያቶች መካከል 13.4 በመቶ የሚሆኑት ስራ ባለማግኘታቸው ምክንያት ተመልሰው ወንጀል ውስጥ መገኘታቸውን ተናግረዋል።
ገንዘብ ለማግኘት አለመቻል እንዲሁም ከማረሚያ ቤት ከወጡ በኋላ ክትትልና ድጋፍ አለመኖርም ተመልሰው በወንጀል ውስጥ እንዲገኙ ማድረጉን የጥናቱ ውጤት ያመለክታል።
በተጨማሪም ከእስር የወጡ ግለሰቦች በማህበረሰቡና በቤተሰቦቻቸው ዘንድ ተቀባይነት ማጣታቸው፣ በማረሚያ ቤቶች ውስጥ በቂ የሙያና የስነ-ልቦና ስልጠና አለመስጠት እንዲሁም በእስር ላይ እያሉ አዳዲስ የወንጀል ስልቶችን መማር በድጋሚ ወንጀል እንዲሰሩ እንዳደረጋቸው ገልጸዋል።
ሌላው በጥናቱ የተጠቀሰው የፌደራል ማረሚያ ቤቶች ወንጀለኞችን በዘመናዊ መንገድ ለመለየት የሚያስችል ወጥና የተደራጀ የዲጂታል መረጃ አያያዝ (Database) ስርዓት አለመኖሩ ሲሆን በተለይም በአዲስ አበባ የፖሊስ ደረጃ የጣት አሻራ ምርመራ በሁሉም ተጠርጣሪዎች ላይ የማይደረግ በመሆኑ፣ ድጋሚ ወንጀል ፈጻሚዎችን ማንነት እና እንደሃገር ያለውን የወንጀል ደጋጋሚነት ምጣኔ በትክክል ለመለየት አስቸጋሪ አድርጎታል ተብሏል።
ጥናቱ ይህንን የፍትህ ስርዓቱን ክፍተት ለማረም የወንጀል ደጋጋሚዎች ከሌሎች ታራሚዎች ተነጥለው ለብቻ የሚያዙበት ራሱን የቻለ የተለየ የተሃድሶ ፕሮግራሞች እንዲኖሩ እንዲሁም የእርምት ጊዜያቸውን ጨርሰው ከማረሚያ ቤት የሚወጡ ታራሚዎች ወደ ማህበረሰቡ መልሶ መቀላቀልን በተመለከተ የተዘጋጀው ረቂቅ ህግ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲጸድቅና ተግባራዊ እንዲሆን ምክረሃሳብ አቅርቧል።
በመድረኩ የተገኙት የፍትህ ሚኒስቴር ተወካይ ጥናቱ የወሰዳቸው የናሙናዎች መጠን (Sample size) አነስተኛ መሆኑን የተናገሩ ሲሆን በምክረ ሃሳብ ደረጃ ለተነሱት ሃሳቦች ግን ረቂቁ ተጠናቅቆ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት መላኩን እና በቅርቡ ይጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ አመልክተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
ነሐሴ 2 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
👉 በጥናቱ ከተካተቱና ወንጀል ፈጽመው ታርመው ከወጡት ታራሚዎች ውስጥ 94 በመቶዎቹ ከ5 አመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ በሌላ ወንጀል በድጋሚ ወደማረሚያ ቤት የተመለሱ ናቸው።
በኢትዮጵያ የወንጀል ፍትህ ሥርዓት ውስጥ ወንጀል ፈጽመው የታረሙ ግለሰቦች በድጋሚ ወደ ወንጀል ድርጊት የመመለሳቸው ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ እንደሚገኝና ይህንን ለመግታት የተቀናጀ የመረጃ አያያዝና የህግ ማዕቀፍ እንደሚያስፈልግ የኢትዮጵያ የህግ እና ፍትህ ኢንስቲትዩት ያከናወነው ጥናት አመልክቷል።
ኢንስቲትዩቱ አመታዊ የጥናትና ምርምር ማጽደቂያ መርሃ ግብሩን ያከናወነ ሲሆን በመድረኩ "የወንጀል ደጋጋሚነት እና የማረሚያ ቤት ሚና በኢትዮጵያ፣ የሕግ ማዕቀፍ እና አተገባበር ስርዓት" የተሰኘ ጥናቱን ይፋ አድርጓል።
በፌደራል ማረሚያ ቤቶች ላይ ትኩረቱን አድርጎ የቀረበው ይህ ጥናት፣ ወንጀለኞች ታርመውና ታንጸው ሰላማዊ ዜጋ እንዲሆኑ ከማድረግ አንጻር አሁንም ሰፊ ክፍተቶች መኖራቸውን አመልክቷል።
ቀደም ሲል በተፈጸመ ወንጀል፣ ቅጣት በተሰጠ ወይም በይቅርታ ቀሪ እንዲሆን በተደረገ በአምስት አመት ጊዜ ውስጥ ስድስት ወር የሚያስቀጣ አዲስ ወንጀል ሰርቶ መገኘት የወንጀል ደጋጋሚነት የሚባል ሲሆን በወንጀል ፍትህ ስርዓት ውስጥ ማረሚያ ቤቶች ታራሚዎችን እያረሙ ስለመሆን ወይም አለመሆናቸው የሚለይበት ዋናኛ መለኪያ ነው።
ይሁን እንጂ በጥናቱ ከተካተቱት 127 የወንጀል ድጋሚ ፈጻሚዎች መካከል ከአምስት ዓመት ቆይታ በኋላ በወንጀል ድርጊት የተገኙት 5.6 በመቶዎቹ ብቻ ሲሆኑ ቀሪዎቹ ማለትም 94.4 በመቶ የሚሆኑት ከአምስት ዓመት በታች በሆነ ጊዜ ወደ ማረሚያ ቤት ተመልሰዋል ይህም የፌደራል ማረሚያ ቤቶች ታራሚዎችን የማረም ሂደት ላይ ውጤታማነት እንደማይታይበት አመላካች ሆኗል።
የጥናቱ ውጤት በዝርዝር ሲታይ 57.9 በመቶ የሚሆኑት ለሁለተኛ ጊዜ ወደ ማረሚያ ቤት የተመለሱ ሲሆኑ፣ 31 በመቶዎቹ ደግሞ ለሦስተኛ ጊዜ የተፈረደባቸው ናቸው።
ከእስር ከተፈቱ በኋላ ወደ ወንጀል ለመመለስ የሚወስድባቸውን ጊዜ በተመለከተ፣ 36.5 በመቶ የሚሆኑት ከ2 እስከ 5 ዓመት ባለው ጊዜ ውስጥ ሲመለሱ፣ 23 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ ከ6 ወር እስከ 1 ዓመት ባለው አጭር ጊዜ ውስጥ በድጋሚ ወንጀል ፈጽመው ይገኛሉ።
17.5 በመቶ የሚሆኑት ደግሞ ከ6 ወር በታች በሆነ ጊዜ ወደ ወንጀል መመለሳቸውን ውጤቱ ያሳያል።
በተጨማሪም፣ ታራሚዎቹ ቀደም ሲል ተከሰው ከተቀጡበት ወንጀል (52 በመቶ ዝርፊያ/ስርቆት) ጀምሮ፣ በአሁኑ ጊዜ ተይዘው ወደ ማረሚያ ቤት እንዲገቡ ካደረጋቸው አዲስ ወንጀል (53.6 በመቶ ዝርፊያ/ስርቆት) ድረስ ተመሳሳይ የወንጀል ዓይነት ደጋግመው መፈጸማቸው በጥናቱ ተመዝግቧል።
የተቀሩት አደንዛዥ ዕፅ መጠቀም እና ማዘዋወር ፣ውንብድና ፣ የግብር ስወራና ማጭበርበር ፣ ህገወጥ የሰዎች ዝውውር ፣የሙስና ወንጀሎች እና ሌሌችም ወንጀሎች ይገኙበታል።
በጥናቱ በድጋሚ ወንጀል እንዲፈጽሙ ካደረጓቸው ምክንያቶች መካከል 13.4 በመቶ የሚሆኑት ስራ ባለማግኘታቸው ምክንያት ተመልሰው ወንጀል ውስጥ መገኘታቸውን ተናግረዋል።
ገንዘብ ለማግኘት አለመቻል እንዲሁም ከማረሚያ ቤት ከወጡ በኋላ ክትትልና ድጋፍ አለመኖርም ተመልሰው በወንጀል ውስጥ እንዲገኙ ማድረጉን የጥናቱ ውጤት ያመለክታል።
በተጨማሪም ከእስር የወጡ ግለሰቦች በማህበረሰቡና በቤተሰቦቻቸው ዘንድ ተቀባይነት ማጣታቸው፣ በማረሚያ ቤቶች ውስጥ በቂ የሙያና የስነ-ልቦና ስልጠና አለመስጠት እንዲሁም በእስር ላይ እያሉ አዳዲስ የወንጀል ስልቶችን መማር በድጋሚ ወንጀል እንዲሰሩ እንዳደረጋቸው ገልጸዋል።
ሌላው በጥናቱ የተጠቀሰው የፌደራል ማረሚያ ቤቶች ወንጀለኞችን በዘመናዊ መንገድ ለመለየት የሚያስችል ወጥና የተደራጀ የዲጂታል መረጃ አያያዝ (Database) ስርዓት አለመኖሩ ሲሆን በተለይም በአዲስ አበባ የፖሊስ ደረጃ የጣት አሻራ ምርመራ በሁሉም ተጠርጣሪዎች ላይ የማይደረግ በመሆኑ፣ ድጋሚ ወንጀል ፈጻሚዎችን ማንነት እና እንደሃገር ያለውን የወንጀል ደጋጋሚነት ምጣኔ በትክክል ለመለየት አስቸጋሪ አድርጎታል ተብሏል።
ጥናቱ ይህንን የፍትህ ስርዓቱን ክፍተት ለማረም የወንጀል ደጋጋሚዎች ከሌሎች ታራሚዎች ተነጥለው ለብቻ የሚያዙበት ራሱን የቻለ የተለየ የተሃድሶ ፕሮግራሞች እንዲኖሩ እንዲሁም የእርምት ጊዜያቸውን ጨርሰው ከማረሚያ ቤት የሚወጡ ታራሚዎች ወደ ማህበረሰቡ መልሶ መቀላቀልን በተመለከተ የተዘጋጀው ረቂቅ ህግ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲጸድቅና ተግባራዊ እንዲሆን ምክረሃሳብ አቅርቧል።
በመድረኩ የተገኙት የፍትህ ሚኒስቴር ተወካይ ጥናቱ የወሰዳቸው የናሙናዎች መጠን (Sample size) አነስተኛ መሆኑን የተናገሩ ሲሆን በምክረ ሃሳብ ደረጃ ለተነሱት ሃሳቦች ግን ረቂቁ ተጠናቅቆ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት መላኩን እና በቅርቡ ይጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ አመልክተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
ነሐሴ 2 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia


