ወደ ይዘቱ ዝለል
ቀጥታ ዝማኔ
ሀሁኒውስ

ግልጽና የታመነ ዜና

“ በዚህ ሰዓት ብሔራዊ ቡድን ማሰልጠን አልፈልግም ” አርነ ስሎት

ምንጭ፦ TIKVAH | Ethiopia Sport

·

አጋራXFacebookTelegramLinkedIn
“ በዚህ ሰዓት ብሔራዊ ቡድን ማሰልጠን አልፈልግም ” አርነ ስሎት
“ በዚህ ሰዓት ብሔራዊ ቡድን ማሰልጠን አልፈልግም ” አርነ ስሎት

አሰልጣኝ አርነ ስሎት በዚህ ሰዓት የኔዘርላንድ ብሔራዊ ቡድንን የመረከብ ፍላጎት እንደሌላቸው አስታውቀዋል።

አሰልጣኙ በአሁኑ ሰዓት ብሔራዊ ቡድን የማሰልጠን ፍላጎት እንደሌላቸው ነው የገለፁት።

“ በዚህ ሰዓት በየቀኑ ከተጨዋቾቼ ጋር መሆን እመርጣለሁ ይሄን በብሔራዊ ቡድን አላገኘውም ” ሲሉ አሰልጣኝ አርነ ስሎት ተናግረዋል።

አክለውም “ ሀገሬን ማሰልጠን ትልቅ ክብር ነው ፤ ነገርግን አሁን ለእኔ ትክክለኛው ጊዜ አይደለም “ ብለዋል።

ከአሰልጣኝ ሮናልድ ኮማን ጋር የተለያየው የኔዘርላንድ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ አርነ ስሎትን ለመሾም ጥያቄ አቅርቦላቸው ነበር።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe

ተዛማጅ ታሪኮች