“ ዋልያዎቹን በነቂስ መጥታችሁ እንደምትደግፉ እምነት አለኝ “ አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ

“ ዋልያዎቹን በነቂስ መጥታችሁ እንደምትደግፉ እምነት አለኝ “ አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ
“ የግብ ጠባቂ እጥረት እየተፈጠረ ነው ”
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ ደጋፊዎች ብሔራዊ ቡድኑን በነቂስ ወጥተው እንዲደግፉ ጥሪ አቅርበዋል።
ዋልያዎቹ በሚቀጥሉት 14 ቀናት ውስጥ ከሱዳን እና ሴኔጋል ጋር የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ያደርጋሉ።
“ ብሔራዊ ቡድኑን በነቂስ መጥታችሁ እንደምትደግፉ እምነት አለኝ “ ሲሉ አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ስለ ግብ ጠባቂዎች ያነሱት አሰልጣኙ “ በአሁኑ ሰዓት የግብ ጠባቂዎች እጥረት እየተፈጠረ ነው ” ሲሉ አሳውቀዋል።
“ በቀጣይ በሊጉ እንኳ ከ 18 ቡድኖች 16ቱ የውጪ ናቸው “ ያሉት አሰልጣኙ “ ክለቦች በዚህ ላይ ተባብረን ብንሰራ ሲሉ ተደምጠዋል።
ትውልደ ኢትዮጵያውያንን በተመለከተ “ መላው አለም የሚጠቀመውን እኛ ለምን እንደማንጠቀም አይገባኝም “ ሲሉ ገልፀዋል።
- ከ 40 በላይ በጀርመን
- ከ 60 በላይ ከ 17-19 ዓመት የሚሆኑ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለኢትዮጵያ መጫወት እንደሚፈልጉ አስረድተዋል።
አክለውም “ ህጎች ተፈፃሚ ሲሆኑ ያሉንን ተጫዋቾች ከ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጋር አጣምረን የተሻለ ብሔራዊ ቡድን በመስራት የተሻለ ውጤት ማምጣት ይቻላል “ ብለዋል።
የኢትዮጵያ ህገ-መንግሥት ጥምር ዜግነት የማይፈቅድ በመሆኑ ትውልደ ኢትዮጵያዊያንን በብሔራዊ ቡድኑ ማካተት አለመቻሉ ይታወቃል።
የካፍ እና ፊፋ ደንብ አንድ ተጨዋች ብሔራዊ ቡድን ለመወከል የሀገሩን ፓስፖርት ይዞ እንዲገኝ ያስገድዳል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
“ የግብ ጠባቂ እጥረት እየተፈጠረ ነው ”
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ ደጋፊዎች ብሔራዊ ቡድኑን በነቂስ ወጥተው እንዲደግፉ ጥሪ አቅርበዋል።
ዋልያዎቹ በሚቀጥሉት 14 ቀናት ውስጥ ከሱዳን እና ሴኔጋል ጋር የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ያደርጋሉ።
“ ብሔራዊ ቡድኑን በነቂስ መጥታችሁ እንደምትደግፉ እምነት አለኝ “ ሲሉ አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ስለ ግብ ጠባቂዎች ያነሱት አሰልጣኙ “ በአሁኑ ሰዓት የግብ ጠባቂዎች እጥረት እየተፈጠረ ነው ” ሲሉ አሳውቀዋል።
“ በቀጣይ በሊጉ እንኳ ከ 18 ቡድኖች 16ቱ የውጪ ናቸው “ ያሉት አሰልጣኙ “ ክለቦች በዚህ ላይ ተባብረን ብንሰራ ሲሉ ተደምጠዋል።
ትውልደ ኢትዮጵያውያንን በተመለከተ “ መላው አለም የሚጠቀመውን እኛ ለምን እንደማንጠቀም አይገባኝም “ ሲሉ ገልፀዋል።
- ከ 40 በላይ በጀርመን
- ከ 60 በላይ ከ 17-19 ዓመት የሚሆኑ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለኢትዮጵያ መጫወት እንደሚፈልጉ አስረድተዋል።
አክለውም “ ህጎች ተፈፃሚ ሲሆኑ ያሉንን ተጫዋቾች ከ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጋር አጣምረን የተሻለ ብሔራዊ ቡድን በመስራት የተሻለ ውጤት ማምጣት ይቻላል “ ብለዋል።
የኢትዮጵያ ህገ-መንግሥት ጥምር ዜግነት የማይፈቅድ በመሆኑ ትውልደ ኢትዮጵያዊያንን በብሔራዊ ቡድኑ ማካተት አለመቻሉ ይታወቃል።
የካፍ እና ፊፋ ደንብ አንድ ተጨዋች ብሔራዊ ቡድን ለመወከል የሀገሩን ፓስፖርት ይዞ እንዲገኝ ያስገድዳል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe


