ወደ ይዘቱ ዝለል
ቀጥታ ዝማኔ
ሀሁኒውስ

ግልጽና የታመነ ዜና

“ ለአሜሪካ ግብር ከፋዮች ፍትሀዊ ውድድር ማረጋጋጥ ነበረብን ”

ምንጭ፦ TIKVAH | Ethiopia Sport

·

አጋራXFacebookTelegramLinkedIn
“ ለአሜሪካ ግብር ከፋዮች ፍትሀዊ ውድድር ማረጋጋጥ ነበረብን ”
“ ለአሜሪካ ግብር ከፋዮች ፍትሀዊ ውድድር ማረጋጋጥ ነበረብን ”

የአሜሪካ የአለም ዋንጫ አዘጋጅ ሀላፊ አንድሪው ጁሊያኒ ስለ ባሎጉን ቀይ ካርድ መሰረዝ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

ሀላፊው ቀይ ካርዱ እንዲሰረዝ ያደረግነው ፍትሀዊ ውድድር እንዲኖር ያለብንን ሀላፊነት ለመወጣት ነው ብለዋል።

“ ቀድሞውን ዳኛው በብራዚል በቀይ ካርድ ጉዳይ ምርመራ ላይ ነው ” ያሉት ሀላፊው “ ቫርን አላግባብ ተጠቅሟል ” ሲሉ ወቅሰዋል።

“ ለውድድሩ ቢሊዮን ዶላር ላወጡት የአሜሪካ ግብ ከፋዮች ፍትሀዊ ውድድር ማረጋገጥ የእኛ ሀላፊነት ነው ” ሲሉ ጨምረው ተናግረዋል።

አክለውም " እርምጃ መውሰድ ነበረብን ሜዳ ላይም ከሜዳ ውጪም ፍትሀዊ ውድድር እንዲሆን ነው " ብለዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe

ተዛማጅ ታሪኮች