ወደ ይዘቱ ዝለል
ቀጥታ ዝማኔ
ሀሁኒውስ

ግልጽና የታመነ ዜና

“ ቡድኑን ለማሻሻል እየሰራን ነው ” ሚኬል አርቴታ

ምንጭ፦ TIKVAH | Ethiopia Sport

·

አጋራXFacebookTelegramLinkedIn
“ ቡድኑን ለማሻሻል እየሰራን ነው ” ሚኬል አርቴታ
“ ቡድኑን ለማሻሻል እየሰራን ነው ” ሚኬል አርቴታ

የመድፈኞቹ አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ ቡድኑን ለማሻሻል እየተሰራ መሆኑን በሰጡት አስተያየት ገልጸዋል።

“ በዝውውር መስኮቱ በንቃት እየሰራን ነው ” ያሉት አርቴታ “ ቡድኑን ለማሻሻል እና ለመገንባት እየሰራን ነው “ ሲሉ ተደምጠዋል።

“ በቀጣይ ሳምንታት እንቅስቃሴ ይጠበቃል ምክንያቱም እንደ ሌሎች ቡድኖች የተሻልን መሆን አለብን “ ሲሉ አክለዋል።

አክለውም “ ተፎካካሪዎቻችን ትልቅ ነገር እያደረጉ ነው “ ያሉ ሲሆን “ እኛም ቆመን አንመለከትም የምንመኘውን የማሳካት ፍላጎት አለን “ ብለዋል።

ምክንያቱም “ ልዩነቱ በጣም ጠባብ ነው ፤ ቡድኑን ማሻሻል እንፈልጋለን ምክንያቱም የፉክክሩ ደረጃ ከፍ ብሏል “ ሲሉ ገልጸዋል።

ስለ ቪንሰስ ጁኒየር ፊርማ ጥያቄ የቀረበላቸው ሚኬል አርቴታ “ አመሰግናለሁ “ ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe

ተዛማጅ ታሪኮች