ወደ ይዘቱ ዝለል
ቀጥታ ዝማኔ
ሀሁኒውስ

ግልጽና የታመነ ዜና

“ አሜሪካን መቼም ማሰልጠን አልፈልግም ” ጄሴ ማርሽ

ምንጭ፦ TIKVAH | Ethiopia Sport

·

አጋራXFacebookTelegramLinkedIn
“ አሜሪካን መቼም ማሰልጠን አልፈልግም ” ጄሴ ማርሽ
“ አሜሪካን መቼም ማሰልጠን አልፈልግም ” ጄሴ ማርሽ

“ ሞሮኮ ምንም ድክመት የላትም ”


አሜሪካዊው የካናዳ አሰልጣኝ ጄሴ ማርሽ የሀገራቸውን ብሔራዊ ቡድን ማሰልጠን እንደማይፈልጉ አሳውቀዋል።

“ የአሜሪካ ብሔራዊ ቡድንን አላሰለጥንም ” ያሉት ጄሴ ማርሽ “ እድል ነበረኝ ነገርግን አሁን አብቅቷል ግድ አይሰጠኝም “ ሲሉ ተደምጠዋል።

“ ቢሆንም ለእነሱ መጥፎ ነገር አልመኝም አሜሪካ ጥሩ እንድትሰራ እፈልጋለሁ “ ሲሉ ጨምረው ተናግረዋል ።

“ አሜሪካዊ በመሆኔ እኮራለሁ ፤ ነገርግን የሌላ ሀገር ነዋሪ ነኝ አሜሪካ አልኖርም ” ጄሴ ማርሽ

ስለ ምሽቱ የሞሮኮ ጨዋታ ያነሱት ጄሴ ማርሽ “
ይሄ የሞሮኮ ቡድን ድክመት እንደሌለው ለቡድኑ ተናግሬያለሁ “ ብለዋል።

“ እኛ ጥሩ በሆንበት ነገር ላይ የተሻለ ሆነን መቅረብ አለብን “ ሲሉ ቡድናቸውን አሳስበዋል።

አክለውም “ ሀሳባችን ሞሮኮ በኳታር ላደረሰችብን ሽንፈት መበቀል ሳይሆን ፤ እነሱን እንዴት እናሸንፋለን የሚለው ነው "ብለዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe

ተዛማጅ ታሪኮች