ኢትዮጵያ የመጀመሪያ ወርቅ አሳካች !

ኢትዮጵያ የመጀመሪያ ወርቅ አሳካች !
በአለም አትሌቲክስ ከ 20ዓመት በታች ሻምፒዮና ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳልያ አግኝታለች።
በሴቶች 3000ሺ ሜትር መሰናክል ፍፃሜ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ተከታትለው ገብተዋል።
አትሌት አልማዝ ዮሀንስ ውድድሯን 9:15.81 በሆነ ሰዓት በአንደኝነት በማጠናቀቅ ለሀገሯ የመጀመሪያውን ወርቅ አስገኝታለች።
እንዲሁም አትሌት ወሰኔ አሰፋ 9:30.50 በሆነ ሰዓት ሁለተኛ ደረጃ ይዛ በማጠናቀቅ የብር ሜዳልያ አሸንፋለች።
አትሌት ወሰኔ አሰፋ የአመቱን ምርጥ ሰዓቷን በማስመዝገብ አጠናቃለች።
ኢትዮጵያ እስካሁን በውድድሩ አንድ የወርቅ ፣ ሁለት የብር እና አንድ የነሀስ ሜዳልያ አግኝታለች።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
በአለም አትሌቲክስ ከ 20ዓመት በታች ሻምፒዮና ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳልያ አግኝታለች።
በሴቶች 3000ሺ ሜትር መሰናክል ፍፃሜ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ተከታትለው ገብተዋል።
አትሌት አልማዝ ዮሀንስ ውድድሯን 9:15.81 በሆነ ሰዓት በአንደኝነት በማጠናቀቅ ለሀገሯ የመጀመሪያውን ወርቅ አስገኝታለች።
እንዲሁም አትሌት ወሰኔ አሰፋ 9:30.50 በሆነ ሰዓት ሁለተኛ ደረጃ ይዛ በማጠናቀቅ የብር ሜዳልያ አሸንፋለች።
አትሌት ወሰኔ አሰፋ የአመቱን ምርጥ ሰዓቷን በማስመዝገብ አጠናቃለች።
ኢትዮጵያ እስካሁን በውድድሩ አንድ የወርቅ ፣ ሁለት የብር እና አንድ የነሀስ ሜዳልያ አግኝታለች።
@tikvahethsport @kidusyoftahe


