ወደ ይዘቱ ዝለል
ቀጥታ ዝማኔ
ሀሁኒውስ

ግልጽና የታመነ ዜና

“ የነበረኝ ቆይታ በምንም አይታወስም ” ማርሴሎ ቤልሳ

ምንጭ፦ TIKVAH | Ethiopia Sport

·

አጋራXFacebookTelegramLinkedIn
“ የነበረኝ ቆይታ በምንም አይታወስም ” ማርሴሎ ቤልሳ
“ የነበረኝ ቆይታ በምንም አይታወስም ” ማርሴሎ ቤልሳ

“ ተጨዋቾቹን ማሻሻል አልቻልኩም አዝኛለሁ ”

ከዩራጓይ የአለም ዋንጫ ስንብት በኋላ አሰልጣኝ ማርሴሎ ቤልሳ ራሳቸውን መቆጣጠር ተስኗቸው ሲበሳጩ ታይተዋል።

“ ለዩራጓይ እግርኳስ ምንም ነገር ሳላበረክት እለቃለሁ “ ያሉት ቤልሳ “ ተጨዋቾቹን ማሻሻል አልቻልኩም አዝኛለሁ “ ሲሉ ተደምጠዋል።

እዚህ የነበረህ ቆይታ በምን ይታወሳል “ ካላችሁኝ በምንም አይታወስም ነው ምላሼ “ ሲሉ ገልጸዋል።

ስለ ቅያሬዎች የተጠየቁት ማርሴሎ ቤልሳ “ ሙስሌራ ራሱ ቀይረኝ ብሎኝ ነው ቫልቬርዴ ግን ማጥቃት ስለፈለኩ ነው ያስወጣሁት “ ብለዋል።

አሰልጣኝ ማርሴሎ ቤልሳ ሶስተኛ የአለም ዋንጫ ተሳትፎ ሲያደርጉ በሁለቱ ቡድናቸውን ከምድብ ማሳለፍ አልቻሉም።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe

ተዛማጅ ታሪኮች