“ የዳኞች ማህበር እንኳን ደስ አላችሁ ” ጆዜ ሞሪንሆ

“ የዳኞች ማህበር እንኳን ደስ አላችሁ ” ጆዜ ሞሪንሆ
የሪያል ማድሪዱ አሰልጣኝ ጆዜ ሞሪንሆ ከደርቢው ሽንፈት በኋላ የጨዋታው ዳኞች ላይ ጠንካራ ትችት ሰንዝረዋል።
ጆዜ ሞሪንሆ ከጨዋታው በኋላ በሰጡት ቃል “ ይህንን ዳኛ የመደባችሁ የዳኞች ኮሚቴ እንኳን ደስ አላችሁ "ሲሉ ገልጸዋል።
የዳኛው ማንነት የሚገለጸው ከጨዋታው 24ሰዓት በፊት መሆኑን ያስረዱት ሞሪንሆ “ ከሳምንት በፊት መታወቁ እንግዳ ነገር ነው ” ብለዋል።
“ ዳኛው ጨዋታውን መዳኘት አይገባውም “ ያሉት አሰልጣኙ “ እሱ አንድም አለም አቀፍ ጨዋታ አልዳኘም ለምን ካላችሁ አቅም የለውም “ብለዋል።
ስለ ሊጉ ዋንጫ ፉክክር የተጠየቁት ጆዜ ሞሪንሆ “ ብቻችንን የምትተዉን ከሆነ ጊዜ አለ ገና "ሲሉ መልሰዋል።
አሰልጣኝ ጆዜ ሞሪንሆ አክለውም “ ዳኞች እባካችሁ እንድንፎካከር ፍቀዱልን ” ሲሉ ጠይቀዋል።
ሪያል ማድሪድን ያስቆጣው አንዱ ጥፋት የተሰራበት ቫልቬርዴ ለሶስት ሳምንታት ከሜዳ እንደሚርቅ ተገልጿል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
የሪያል ማድሪዱ አሰልጣኝ ጆዜ ሞሪንሆ ከደርቢው ሽንፈት በኋላ የጨዋታው ዳኞች ላይ ጠንካራ ትችት ሰንዝረዋል።
ጆዜ ሞሪንሆ ከጨዋታው በኋላ በሰጡት ቃል “ ይህንን ዳኛ የመደባችሁ የዳኞች ኮሚቴ እንኳን ደስ አላችሁ "ሲሉ ገልጸዋል።
የዳኛው ማንነት የሚገለጸው ከጨዋታው 24ሰዓት በፊት መሆኑን ያስረዱት ሞሪንሆ “ ከሳምንት በፊት መታወቁ እንግዳ ነገር ነው ” ብለዋል።
“ ዳኛው ጨዋታውን መዳኘት አይገባውም “ ያሉት አሰልጣኙ “ እሱ አንድም አለም አቀፍ ጨዋታ አልዳኘም ለምን ካላችሁ አቅም የለውም “ብለዋል።
ስለ ሊጉ ዋንጫ ፉክክር የተጠየቁት ጆዜ ሞሪንሆ “ ብቻችንን የምትተዉን ከሆነ ጊዜ አለ ገና "ሲሉ መልሰዋል።
አሰልጣኝ ጆዜ ሞሪንሆ አክለውም “ ዳኞች እባካችሁ እንድንፎካከር ፍቀዱልን ” ሲሉ ጠይቀዋል።
ሪያል ማድሪድን ያስቆጣው አንዱ ጥፋት የተሰራበት ቫልቬርዴ ለሶስት ሳምንታት ከሜዳ እንደሚርቅ ተገልጿል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe


