ወደ ይዘቱ ዝለል
ቀጥታ ዝማኔ
ሀሁኒውስ

ግልጽና የታመነ ዜና

“ የጊዜ ጉዳይ ነው የአፍሪካ ሀገር አለም ዋንጫ ያሸንፋል ”

ምንጭ፦ TIKVAH | Ethiopia Sport

·

አጋራXFacebookTelegramLinkedIn
“ የጊዜ ጉዳይ ነው የአፍሪካ ሀገር አለም ዋንጫ ያሸንፋል ”
“ የጊዜ ጉዳይ ነው የአፍሪካ ሀገር አለም ዋንጫ ያሸንፋል ”

የዲሞክራቲክ ኮንጎ አሰልጣኝ ሴባስቲያን ዲሳብሬ የአፍሪካ እግር ኳስ እየተሻሻለ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

“ አፍሪካ እየተሻሻለች ነው አትቆምም “ ያሉት አሰልጣኙ “ የአፍሪካ ሀገር በዚህ አመት ወይም በቀጣይ አለም ዋንጫ እንደሚያሸንፍ ተስፋ አደርጋለሁ ” ብለዋል።

“ የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ የአፍሪካ ሀገር ዓለም ዋንጫ ያሸንፋል “ ሲሉ ፈረንሳዊው አሰልጣኝ ሴባስቲያን ዲሳብሬ ተናግረዋል።

አክለውም “ በአለም ዋንጫው አፍሪካ ብዙ ተሳታፊ ሊኖራት ይገባል ምክንያቱም እግርኳስ የአህጉሪቱ እስትንፋስ ነው “ብለዋል።

ዲሞክራቲክ ኮንጎ ዛሬ ኡዝቤክስታን የምታሸንፍ ከሆነ ወደ ጥሎ ማለፉ መቀላቀሏን ታረጋግጣለች።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe

ተዛማጅ ታሪኮች