ወደ ይዘቱ ዝለል
ቀጥታ ዝማኔ
ሀሁኒውስ

ግልጽና የታመነ ዜና

የ ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ፍፃሜውን አገኘ !

ምንጭ፦ TIKVAH | Ethiopia Sport

·

አጋራXFacebookTelegramLinkedIn
የ ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ፍፃሜውን አገኘ !
የ ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ፍፃሜውን አገኘ !

ሲዳማ ቡና ሻምፒዮን የሆነበት የ 2018 የ ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ፍፃሜውን አግኝቷል።

በሀዋሳ ከተማ በተደረገው የመጨረሻ ጨዋታ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ሲዳማ ቡናን 1ለ0 አሸንፏል።

ሻምፒዮኑ ሲዳማ ቡና 6️⃣8️⃣ ነጥቦችን በመሰብሰብ አመቱን አጠናቋል።

ኢትዮ ኤሌክትሪክ በ 5️⃣4️⃣ ነጥቦች አምስተኛ ደረጃ በመያዝ ማጠናቀቅ ችለዋል።

ሲዳማ ቡና ከደቂቃዎች በኋላ የመጀመሪያውን የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫ የሚረከብ ይሆናል።

ኮከብ ግብ አግቢዎች እነማን ናቸው ?

- ታምራት እያሱ ( ፋሲል ከነማ )
- ናትናኤል ዳንኤል ( ንግድ ባንክ ) በ 1️⃣5️⃣ ጎል ኮከብ ግብ አግቢ ሆነው አጠናቀዋል።

እነማን ወረዱ ?

- ሽረ ምድረ ገነት
- ድሬዳዋ ከተማ
- መቐለ 70 እንደርታ እና
- አርባምንጭ ከተማ ወደ ከፍተኛ ሊግ የወረዱ ክለቦች ሆነዋል።

እነማን ወደ ፕሪሚየር ሊጉ አደጉ ?

- ጋሞ ጨንቻ እና
- ሀላባ ከተማ ወደ 2019 ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አድገዋል።

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በሚቀጥለው የውድድር አመት በ 1️⃣8️⃣ ክለቦች መካከል የሚደረግ ይሆናል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe

ተዛማጅ ታሪኮች