#France
ምንጭ፦ TIKVAH Ethiopia
·

#France
#Paris
በፈረንሳይ፣ ፓሪስ ከተማ " የግብረሰዶማውያን ማህበር ፕሬዚዳንት " እንደሆነ የተነገረለት እና እራሱም የፖሊስ መኮንን የሆነው ፒየር ፒካቬት የተባለ ግለሰብ በጠርሙስ ተቀጥቅጦ ጉዳት ደርሶበት ሆስፒታል መግባቱን ከፍራንስ 24 ዘገባ ተመልክተናል።
ፒካቬት በፓሪስ መሃል በሚገኘው ማራይስ አካባቢ ከአንድ ባር ከወጣ በኋላ በአንድ ግለሰብ በጠርሙስ መቀጥቀጡ ተገልጿል።
ጥቃቱ በሰውነቱ ላይ በርካታ ጉዳቶችን እንዲደርስበት ያደረገ ሲሆን የውስጥ ደም መፍሰስና የጭንቅላት ቁስልም እንደደረሰበት ተዘግቧል።
ፓሪስ ውስጥ የግብረሰዶማውያን መብት ተሟጋች ማህበር ፕሬዝዳንት የሆነው ፒካቬት እራሱን የፖሊስ መኮንን መሆኑን በመግለጽ የፖሊስ መታወቂያውን ቢያሳይም፣ ተጠርጣሪው ጥቃቱን እንዳላቆመ ተመላክቷል።
በጥቃቱ ወቅትም ጥቃት አድራሹ " አጸያፊ ነው " ስላለው የግብረሰዶማዊነት ተግባር በስድብና በኃይለ ቃል ግለሰቡን ሲናገረው እንደነበር ተመላክቷል።
ተጠርጣሪው በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን ከዚህ በፊት የወንጀል መዝገብ እንደሌለው ተገልጿል።
የፓሪስ ከንቲባ ኤማኑኤል ግሬጎዋር ጥቃቱን አውግዘዋል። " ፓሪስ ለሁሉም ሰዎች የነፃነትና የደህንነት ከተማ ሆና ትቀጥላለች " ሲሉ መናገራቸው ነው የተሰማው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ነሐሴ 26 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
#Paris
በፈረንሳይ፣ ፓሪስ ከተማ " የግብረሰዶማውያን ማህበር ፕሬዚዳንት " እንደሆነ የተነገረለት እና እራሱም የፖሊስ መኮንን የሆነው ፒየር ፒካቬት የተባለ ግለሰብ በጠርሙስ ተቀጥቅጦ ጉዳት ደርሶበት ሆስፒታል መግባቱን ከፍራንስ 24 ዘገባ ተመልክተናል።
ፒካቬት በፓሪስ መሃል በሚገኘው ማራይስ አካባቢ ከአንድ ባር ከወጣ በኋላ በአንድ ግለሰብ በጠርሙስ መቀጥቀጡ ተገልጿል።
ጥቃቱ በሰውነቱ ላይ በርካታ ጉዳቶችን እንዲደርስበት ያደረገ ሲሆን የውስጥ ደም መፍሰስና የጭንቅላት ቁስልም እንደደረሰበት ተዘግቧል።
ፓሪስ ውስጥ የግብረሰዶማውያን መብት ተሟጋች ማህበር ፕሬዝዳንት የሆነው ፒካቬት እራሱን የፖሊስ መኮንን መሆኑን በመግለጽ የፖሊስ መታወቂያውን ቢያሳይም፣ ተጠርጣሪው ጥቃቱን እንዳላቆመ ተመላክቷል።
በጥቃቱ ወቅትም ጥቃት አድራሹ " አጸያፊ ነው " ስላለው የግብረሰዶማዊነት ተግባር በስድብና በኃይለ ቃል ግለሰቡን ሲናገረው እንደነበር ተመላክቷል።
ተጠርጣሪው በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን ከዚህ በፊት የወንጀል መዝገብ እንደሌለው ተገልጿል።
የፓሪስ ከንቲባ ኤማኑኤል ግሬጎዋር ጥቃቱን አውግዘዋል። " ፓሪስ ለሁሉም ሰዎች የነፃነትና የደህንነት ከተማ ሆና ትቀጥላለች " ሲሉ መናገራቸው ነው የተሰማው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ነሐሴ 26 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia


