በአፋን ኦሮሞ ሙዚቃዎቿ የምትታወቀው አንጋፋዋ አርቲስት እልፍነሽ ቀኖ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች።
ምንጭ፦ TIKVAH Ethiopia
·

በአፋን ኦሮሞ ሙዚቃዎቿ የምትታወቀው አንጋፋዋ አርቲስት እልፍነሽ ቀኖ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች።
የኦሮሚያ ክልል " አርቲስት እልፍነሽ ለበርካታ ዓመታት በተለይም በትግል ዘፈኖቿና በግጥሞቿ ለኦሮሞ ሕዝብ መብት ስትታገል ቆይታለች " ብሏል።
" አርቲስቷ የጥበብን ኃይል በመጠቀም በሕዝባዊ ትግል ውስጥ ከፍተኛ ሚና በመጫወት በቀዳሚነት ከሚጠቀሱ ድምጻውያን መካከል ናት " ሲል ገልጿል።
በምሥራቅ ወለጋ ዞን ነቀምቴ ከተማ አቅራቢያ በምትገኘው ሲቡ ጉቶ በተባለች ስፍራ የተወለደችው እልፍነሽ በ1969 ወደ ትግል በመቀላቀል ከዚያ ጊዜ ጀምሮ በሥነ-ጥበብ ሥራዎቿ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክታለች።
ለበርካታ ዓመታት ከኖረችበት ኖርዌይ በቅርቡ ወደ ሀገሯ የተመለሰች ሲሆን፤ ባደረባት ሕመም በህክምና ስትረዳ ቆይታ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች፡፡
ጳጉሜን 1 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
የኦሮሚያ ክልል " አርቲስት እልፍነሽ ለበርካታ ዓመታት በተለይም በትግል ዘፈኖቿና በግጥሞቿ ለኦሮሞ ሕዝብ መብት ስትታገል ቆይታለች " ብሏል።
" አርቲስቷ የጥበብን ኃይል በመጠቀም በሕዝባዊ ትግል ውስጥ ከፍተኛ ሚና በመጫወት በቀዳሚነት ከሚጠቀሱ ድምጻውያን መካከል ናት " ሲል ገልጿል።
በምሥራቅ ወለጋ ዞን ነቀምቴ ከተማ አቅራቢያ በምትገኘው ሲቡ ጉቶ በተባለች ስፍራ የተወለደችው እልፍነሽ በ1969 ወደ ትግል በመቀላቀል ከዚያ ጊዜ ጀምሮ በሥነ-ጥበብ ሥራዎቿ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክታለች።
ለበርካታ ዓመታት ከኖረችበት ኖርዌይ በቅርቡ ወደ ሀገሯ የተመለሰች ሲሆን፤ ባደረባት ሕመም በህክምና ስትረዳ ቆይታ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታለች፡፡
ጳጉሜን 1 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia

