ወደ ይዘቱ ዝለል
ቀጥታ ዝማኔ
ሀሁኒውስ

ግልጽና የታመነ ዜና

“ ኢራን ስትሰናበት በደስታ ጨፍሪያለሁ ” የአሜሪካ ባለስልጣን

ምንጭ፦ TIKVAH | Ethiopia Sport

·

አጋራXFacebookTelegramLinkedIn
“ ኢራን ስትሰናበት በደስታ ጨፍሪያለሁ ” የአሜሪካ ባለስልጣን
“ ኢራን ስትሰናበት በደስታ ጨፍሪያለሁ ” የአሜሪካ ባለስልጣን

“ ድርጊቱ ያለውን የአስተሳሰብ ማነስ ያሳያል ”  ኢራን


የአሜሪካ የመንግሥት ሀላፊ ማርክዋይኔ ሙሊን ኢራን ከአለም ዋንጫ መሰናበት አስጨፍሮኛል በማለት ተናግረዋል።

የሀገሪቱ ሆምላንድ ሴኩሪቲ ሴክሬታሪ ማርክዋይኔ ሙሊን በሰጡት ቃል “ እነሱ ወደዚህ ተመልሰው ስለማይመጡ ደስተኛ ነኝ ” ሲሉ ተደምጠዋል።

“ ቪዛቸውን ቀምተን ከአሜሪካ ምድር መውጣት አለባችሁ ስንላቸው ደስተኛ ነበርኩ “ ሲሉ ፖለቲከኛው ጨምረው ተናግረዋል።

አክለውም “ ከውድድሩ በመባረራቸው ደስተኛ ነኝ ከተሰናበቱ በኋላም በደስታ ጨፍሪያለሁ ” ብለዋል።

የኢራን እግርኳስ ፌዴሬሽን በበኩሉ በሰጠው ምላሽ “ ኢራናውያን የአሜሪካን ጥሩ ያልሆነ አቀባበል እና ውሸት ስለለመዱ ንግግሩ አላስገረማቸውም “ ብሏል።

“ ንግግሩ አሜሪካ አለም አቀፍ ህግ እንደማታከብር ያረጋገጠ ነው “ ያለችው ኢራን “ አዘጋጅ ሀገር ማድረግ ያለበትን ደንብ አላከበሩም “ ብላለች።

“ ኢራን ስትባረር መጨፈሩ ስለ እኛ ቡድን ሳይሆን ስለእሱ ብዙ ይናገራል ፤ ትንሽ አስተሳሰብ እንዳለው ያሳያል ” ኢራን

@tikvahethsport     @kidusyoftahe

ተዛማጅ ታሪኮች