ወደ ይዘቱ ዝለል
ቀጥታ ዝማኔ
ሀሁኒውስ

ግልጽና የታመነ ዜና

“ እንደምናልፍ እናውቅ ነበር “ አሽራፍ ሀኪሚ

ምንጭ፦ TIKVAH | Ethiopia Sport

·

አጋራXFacebookTelegramLinkedIn
“ እንደምናልፍ እናውቅ ነበር “ አሽራፍ ሀኪሚ
“ እንደምናልፍ እናውቅ ነበር “ አሽራፍ ሀኪሚ

“ የወከልነው አፍሪካን ነው “

የሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን አምበል አሽራፍ ሀኪሚ “ ቀጣዩን ዙር እንደምንቀላቀል እናውቅ ነበር “ ሲል ተደምጧል።

አሽራፍ ሀኪሚ ይህን ያለበት ምክንያት ሲናገር “ ምክንያቱም እኛ ግብ ጠባቂያችን ያሲን ቦኖ አለልን “ ሲል ተናግሯል።

በቡድን ጓደኞቹ መኩራቱን የገለፀው ሀኪሚ “ የወከልነው የአፍሪካን እግር ኳስ ነው ፣ በእኛ እንዲኮሩ እናደርጋለን “ ብሏል።

በእድል የመጣ ውጤት እንዳልሆነ የገለፀው አሽራፍ ሀኪሚ “ ብዙ ሰዎች የ 2022 የአለም ዋንጫ ጉዟችን በእድል የተገኘ ይመስላቸዋል “ በማለት ተናግሯል።

ሀኪሚ ለነበረው ድጋፍ ምስጋናውን ሲቸር “ መላውን የሜክሲኮ ህዝብ ላደረጉልን ድጋፍ አመሰግናለሁ “ ብሏል።

@tikvahethsport @kidusyoftahe

ተዛማጅ ታሪኮች