“ ዲዮማንዴን ቀጣይ ተከላካይ እናደርገዋለን ”

“ ዲዮማንዴን ቀጣይ ተከላካይ እናደርገዋለን ”
የሌፕዚጉ የፊት መስመር አጥቂ ያን ድዮማንዴ ስሙ ከሊቨርፑል እና ፒኤስጂ ጋር እያተያያዘ ይገኛል።
ኮትዲቯራዊው አጥቂ ሌፕዚግን የሚለቅ ከሆነ ፒኤስጂ መቀላቀል እንደሚመርጥ እየተዘገበ ይገኛል።
ይሁን እንጂ ፒኤስጂ ተጫዋቹን ለማስፈረም እስካሁን ይፋዊ እንቅስቃሴ አላደረገም።
የሌፕዚግ የስፖርት ዳይሬክተር ማርሴል ሼፈር በበኩላቸው ተጫዋቹ ሊለቅ ነው መባሉን ውድቅ በማድረግ “ ለሽያጭ አይቀርብም “ ብለዋል።
“ ሀሳባችን ዲዮማንዴ በሚቀጥለው አመት የቀኝ መስመር ተከላካይ ሆኖ እንዲጫወት ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
" ተጨዋቹ በዚሁ ከቀጠለ አዲስ ነገር እንዲሞክር አድል እንሰጠዋለን ነገርግን በዚህ አመት አይደለም " ብለዋል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
የሌፕዚጉ የፊት መስመር አጥቂ ያን ድዮማንዴ ስሙ ከሊቨርፑል እና ፒኤስጂ ጋር እያተያያዘ ይገኛል።
ኮትዲቯራዊው አጥቂ ሌፕዚግን የሚለቅ ከሆነ ፒኤስጂ መቀላቀል እንደሚመርጥ እየተዘገበ ይገኛል።
ይሁን እንጂ ፒኤስጂ ተጫዋቹን ለማስፈረም እስካሁን ይፋዊ እንቅስቃሴ አላደረገም።
የሌፕዚግ የስፖርት ዳይሬክተር ማርሴል ሼፈር በበኩላቸው ተጫዋቹ ሊለቅ ነው መባሉን ውድቅ በማድረግ “ ለሽያጭ አይቀርብም “ ብለዋል።
“ ሀሳባችን ዲዮማንዴ በሚቀጥለው አመት የቀኝ መስመር ተከላካይ ሆኖ እንዲጫወት ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
" ተጨዋቹ በዚሁ ከቀጠለ አዲስ ነገር እንዲሞክር አድል እንሰጠዋለን ነገርግን በዚህ አመት አይደለም " ብለዋል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe


