ወደ ይዘቱ ዝለል
ቀጥታ ዝማኔ
ሀሁኒውስ

ግልጽና የታመነ ዜና

#TeamEthiopia 🇪🇹

ምንጭ፦ TIKVAH | Ethiopia Sport

·

አጋራXFacebookTelegramLinkedIn
#TeamEthiopia 🇪🇹
#TeamEthiopia 🇪🇹

የኢትዮጵያ ከ 17ዓመት በታች የሴቶች ብሔራዊ ቡድን ወሳኝ መርሐ ግብሩን ዛሬ ከቀኑ 9:00 ከ ዛምቢያ አቻው ጋር ያደርጋል።

ብሔራዊ ቡድኑ 90 ደቂቃውን በአሸናፊነት ከተወጣ በሞሮኮው የአለም ዋንጫ ተሳታፊ መሆኑን ያረጋግጣል።

አሰልጣኝ ራውዲ አሊ “ በትኩረት ለመጫወት ዝግጁ ነን “ ያለች ሲሆን “ የኢትዮጵያ ህዝብ እግር ኳስ ወዳድ ነው መጥቶ እንዲደግፈን ጥሪ አቀርባለሁ “ ብላለች።

በመጀመሪያው ዙር ጨዋታ ዛምቢያ 2ለ1 በሜዳዋ ያሸነፈች ሲሆን በድምር ውጤት የሚያሸንፈው ሀገር ለአለም ዋንጫው ማለፉን ያረጋግጣል።

ጨዋታው 9:00 በአበበ በቂላ ስታዲየም ሲካሄድ ስፖርት አፍቃሪው ስታዲየም በመገኘት በነፃ እንዲደግፍ ጥሪ ቀርቧል።

@tikvahethsport @kidusyoftahe

ተዛማጅ ታሪኮች