“ እኔን እንዲተካ የሾምኩት ሞሪንሆን ነበር ” ፈርጉሰን

“ እኔን እንዲተካ የሾምኩት ሞሪንሆን ነበር ” ፈርጉሰን
የቀድሞ የማንችስተር ዩናይትድ ታሪካዊ አሰልጣኝ ሰር አሌክስ ፈርጉሰን ከዚህ በፊት ያልተሰማ ታሪክ ተናግረዋል።
አሰልጣኝ ሰር አሌክስ ፈርጉሰን 2013 ከሀላፊነት ሲለቁ እንዲተኳቸው የተሾሙት ጆዜ ሞሪንሆን እንደነበር ገልጸዋል።
“ ሞሪንሆ እኔን እንዲተካ ጠይቀነው ነበር እኔም ሁሉንም አብራርቼለት ተስማምቶም ነበር “ ሲሉ ሰር አሌክስ ፈርጉሰን ተናግረዋል።
ይሁን እንጂ በአንዱ ምሽት “ እያለቀሰ ደወለልኝ ” የሚሉት ፈርጉሰን “ ማድረግ አልችልም አሌክስ ለቼልሲ ቃሌን ሰጥቻለሁ ማጠፍ አልፈልግም ሲል ነግሮኛል “ ብለዋል።
አክለውም “ የሰጠኝን ምክንያት ተረድቻለሁ ነገርግን በጣም አበሳጭቶኝ ነበር “ ሲሉ አዲስ በወጣው የጆዜ ሞሪንሆ ዘጋቢ ፊልም ላይ ተናግረዋል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
የቀድሞ የማንችስተር ዩናይትድ ታሪካዊ አሰልጣኝ ሰር አሌክስ ፈርጉሰን ከዚህ በፊት ያልተሰማ ታሪክ ተናግረዋል።
አሰልጣኝ ሰር አሌክስ ፈርጉሰን 2013 ከሀላፊነት ሲለቁ እንዲተኳቸው የተሾሙት ጆዜ ሞሪንሆን እንደነበር ገልጸዋል።
“ ሞሪንሆ እኔን እንዲተካ ጠይቀነው ነበር እኔም ሁሉንም አብራርቼለት ተስማምቶም ነበር “ ሲሉ ሰር አሌክስ ፈርጉሰን ተናግረዋል።
ይሁን እንጂ በአንዱ ምሽት “ እያለቀሰ ደወለልኝ ” የሚሉት ፈርጉሰን “ ማድረግ አልችልም አሌክስ ለቼልሲ ቃሌን ሰጥቻለሁ ማጠፍ አልፈልግም ሲል ነግሮኛል “ ብለዋል።
አክለውም “ የሰጠኝን ምክንያት ተረድቻለሁ ነገርግን በጣም አበሳጭቶኝ ነበር “ ሲሉ አዲስ በወጣው የጆዜ ሞሪንሆ ዘጋቢ ፊልም ላይ ተናግረዋል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe


