ወደ ይዘቱ ዝለል
ቀጥታ ዝማኔ
ሀሁኒውስ

ግልጽና የታመነ ዜና

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ለሁለት የሚዲያ ተቋማት የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሰጠ።

ምንጭ፦ TIKVAH Ethiopia

·

አጋራXFacebookTelegramLinkedIn
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ለሁለት የሚዲያ ተቋማት የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሰጠ።
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ለሁለት የሚዲያ ተቋማት የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሰጠ።

ባለሥልጣን መ/ቤቱ፤ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ የሰጣቸው ለአሐዱ ኤፍ ኤም 94.3 እና አርትስ ቴሌቪዥን ነው።

" የሚዲያ ተቋማቱ የተሰጣቸውን የይዘት ግዴታዎች በመተላለፍ ለተከታታይ ጊዜ ያልተረጋገጠ፣ ሚዛናዊ ያልሆነ እና የሕዝብን ጥቅም የሚጎዳ መረጃ በማሰራጨታቸው የመጨረሻ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል " ሲል ነው ያሳወቀው።

" ከሁለቱ ተቋማት ኃላፊዎች ጋር በተደጋጋሚ በታዩ የሕግና የሙያ ጥሰቶች ላይ ውይይት ባድረግም ጉልህ ለውጥ ባለመታየቱ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያው ተሰጥቷል " ብሏል።

" ሁለቱ የሚዲያ ተቋማት በቀጣይ ሥራቸውን በሕግና በሙያ ሥነ ምግባር መሠረት እንዲያከናውኑ " ያሳሰበው ባለሥልጣን መ/ቤቱ የተሰጠውን ማስጠንቀቂያ በመጣስ ተመሳሳይ ጥሰቶች ከቀጠሉ በሕጉ መሠረት ተጨማሪ አስተዳደራዊ እርምጃ እንደሚወሰድ አስጠንቅቋል።

" ሁሉም የሚዲያ ተቋማት በዘገባ ሥራቸው የመገናኛ ብዙኃን አዋጅን፣ የሀገሪቱን ሕጎችና የሙያ ሥነ ምግባርን አክብረው መስራት ግዴታቸው ነው " ሲልም አሳስቧል።

ሃምሌ 24 ቀን 2018 ዓ/ም

@tikvahethiopia

ተዛማጅ ታሪኮች